the green flood

the green flood

Sunday, March 17, 2013

የመስቀል ዓደባባይ አትሌቶች

           በኖቬምበር  ወር 2012 ላይ በመስቀል አደባባይ በኩል  ሳልፍ  በርከት ያሉ  አትሌቶች ደረጃውን  ወደ ላይ ወደ ታች  እየተመላለሱ  ሲለማመዱ  አይቼ  ቀልቤን ስለሳበኝ   ቀረብ  አልኩና  ሰላምታ ከተለዋወጥኩ  በኋላ  ለምታለማምዳቸው   ሴት  አንዳንድ  ጥያቄዎች አቀረብኩ   ለምሳሌ  ያህል    የት ክለብ ናችሁ ?..........
 የማረሚያ  ፖሊስ  አትሌቶች እንደ ሆኑ እና   መስቀል ዓደባባይ  አቅራቢያ ብሆራዊ  ሆቴል  ጂም ናዚየም ለመግባት እያሟሟቁ  እንደሆነ ተረዳሁ  ብዙ  የማውቃቸውን  ሰዎች ስላላየሁ  አሁንም  ጥያቄ አቀረብኩ ፣ የረጅም ርቀት ቡድን  ዛሬ እዚህ ስለማይሰሩ እነሱ የሉም አለችኝ   እመሰግናለሁ  ብዬ   መንገድ    ከጀመርኩ  በኋላ  የህብረት  ጂምናስቲክ  አሰራራቸው   ስለሳበኝ   እና  እትዝታ ስለቀሰቀሰብኝ  አንድ ፎቶ  ለምን አላነሳም ብዬ   ካሜራዬን  ሳስተካክል ከመካከላቸው አንዱ ያዙኝ ልቀቁኝ ኣለ  ምን ሆኖ ነው  ምን  ተከሰተ ብዬ  ማንሳቱን  ኣቋረጥኩ ፣

    በዚህ ግዜ ሌላው  ቀረብ ብሎ  እዚህ አሁን ዲሞክራሲ  ስለሆነ    መናገር እና መከልከል መብቱ ነው  ኣለኝ   ተመስጌን
  ዲሞክራሲን  በዓይኔ አየሁ ብዬ  የነሳሁት ሁለት  ፎቶዎች  እያሳየሁ   ከካሜራዬ ላይ አጥፎቼ   ሄድኩ፣
   በየስታድዮሙ  ካሜራ ኣንግቦ  እየገባ ፎቶ  የሚያነሳው ተመልካች እና  የፕሬስ  ሰው  ሁሉ አትሌቱን  እያስፈቀደ  ኖሮኣል  እንዴ?  እኔን  ግን  ብዙ ሰዎች ብዙ  ጊዜ  ፎቶ  ሲያነሱኝ  እያስፈቀዱኝ ኣልነበረም፣  እናንተስ ???????
ባለካሜራዉ  ምናልባት   ፈረንጅ  ቢሆን ኖሮ  ደጋግመህ አንሳን ብለው እንደሚለምኑት   እገምታለሁ ፣