the green flood

the green flood

Wednesday, March 26, 2008

የኢትዮጵያ፡አትሌቶች፡ንቅናቄ፡1970ዎቹ፡እስከ1984ዓም

በቅርቡ፡የሚወጣ፡ጽሁፍ፡

36ኛው፡የዓለም፡ሃገር፡አቋራጭ፡ሩጫ፡፡በኤዲንበርግ፡ይደረጋል።

እ.ኤ.አ.ማርች፡30/2008ዓ.ም፡ በሚጀመረው፡የዓለም፡ሃገር፡አቋራጭ፡ውድድር፡ከሚሰለፉት፡ሃገሮች፡ውስጥ፡ጠንካራው፡ የኢትዮጵያ፡ቡድን፡መሆኑን፡ብዙዎች፡ይገምታሉ፡በዚህ፡በ36ኛው፡ኤዲንበርጉ፡የዓለም፡ሃገር፡አቋራጭ፡ውድድር፡የኬንያ፡ቡድን፡ቢሳተፍም፡በሃገሪቱ፡በተፈጠረው፡የፖለቲካ፡ውዝግብ፡የተነሳ፡በስነልቦና፡ዝግጅት፡ከቀድሞው፡ባነሰ፡ጥንካሬ፡እንደሚቀርብ፡ይገመታል፡በቅርቡ፡በተደረገው፡የቤት፡ውስጥ፡የዓለም፡ሻምፒዮና፡ይህው፡ታይቶ፡ነበር።

የኤርትራ፡ቡድን፡በጠንካራው፡አትሌት፡ዘረሰናይ፡ታደሰ፡ዘንድሮም፡የአምናውን፡ድል፡ላለማስነጠቅ፡እንደሚተጋ፡ይጠበቃል።በመቀጠል፡የሞሮኮ፡ቡድን፡በሰልጣኝ፡ኢብራሂም፡ቡላሚ፡አማካኝነት፡በአዲስ፡መልክ፡የተመረጡ፡በአብዛኛ፡ወጣት፡የሆኑ፡አትሌቶችን፡ይዞ፡ይሰለፋል።

በዚህ፡ዓመት፡ከኤርትራው፡ዘረሰናይ፡በስተቀር፡ለኢትዮጵያ፡ቡድን፡ሌላ፡የሚያሰጋ፡እንዳሌለ፡ብዙዎች ፡ይተነብያሉ።በቀነኒሳና፡በጥሩነሽ፡የሚመራው፡የኢትዮጵያ፡ቡድን፡ በድል፡እንደሚመለስ፡ይጠበቃል።

Monday, March 24, 2008

የኢትዮጵያ፡አትሌቶች፡የኦሎምፒክ፡ተሳትፎ፡

ኢትዮጵያ፡አትሌቶችን፡ለኦሎምፒክ፡ውድድር፡መላክ፡የጀመርችው፡እንደ፡አውሮፓዊያን፡አቆጣጠር፤በ1956 ዓ.ም፡ ነበር።የመጀመርያው፡የኦሎምፒክ፡ተሳትፎአችን፡የአውስትራሊያው፡ሜልቦርን፡ኦሎምፒክ፡ሲሆን፡ኢትዮጵያ፡በማራቶን፡ውድድር፡አትሌት፡ባሻዬ፡ፈለቀ፡እና፡ብርሃኑን፡አሰለፈች።
እስከ፡አሁንም፡ዓለምን፡እያስደነቀ፡ያለው፡የኢትዮጵያ፡አትሌቶች፡አይበገሬነት፡በሜልቦርን፡ተጀምሮ፡በ1960ዓ.ም፡በሮም፡ኦሎምፒክ፡በአበበ፡ቢቂላ፡ድል፡አድራጊነት፡የመጀመርያው፡የወርቅ፡ሜዳልያ፡ለኢትዮጵያ፡ለአፍሪካ፡በማስገኘት፡ዛሬም፡ላለው፡ድላችን፡በር፡ከፋች፡ሆነ።
በባዶ፡እግሩ፡ማራቶንን፡የሚያክል፡ከባድ፡ውድድር፡በሚያስደንቅ፡ፍጥነት፡የሞሮኮውን፡አትሌት፡ከሗላው፡አስከትሎ፡በመገባት፡የኦሎምፒክ፡ባለ፡ድል፡ከመሆኑም፡ሌላ፡አዲስ፡የዓለም፡የማራቶን፡ክብረወሰን፡ባለቤት፡ሆነ።
የአበበ፡ስም፡እየገነነ፡እና፡በየተሰለፈበት፡ውድድር፡ሁሉ፡ድልን፡እየተቀዳጀ፡መጣ፡ አይደርስ፡የለምና፡ አራት፡ዓመት፡ቆይቶ፡በ1964ዓ.ም፡ የጃፓኑ፡ቶክዮ፡ኦሎምፒክ፡ደረሰ፡አሁንም፡ሞት፡እንጂ፡ሰው፡ያላሸነፈው፡አበበ፡ቢቂላ፡የሁሉንም፡ሃገር፡አትሌቶች፡ቀድሞ፡በመግባት፡ለእናት፡ሃገሩ፡ሁለተኛውን፡የወርቅ፡ሜዳልያ፡ከአዲስ፡የማራቶን፡ክብረወሰን፡ጋር፡አስገኘ።
አበበ፡ሁለተኛውን፡ኦሎምፒክ፡ስያሸንፍ፡የትርፍ፡አንጀት፡ቀዶ፡ጥገና፡አድርጎ፡ከሆስፒታል፡ከወጣ፡በጥቂት፡ሳምንታት፡ውስጥ፡መሆኑ፡ሌላው፡አስደናቂ፡ታሪክ፡ሆነ።
ከሮም፡ኦሎምፒክ፡ወቅት፡ጀምሮ፡በስዊዲናዊው፡ማጆር፡ኦኒስ፡ኒስካንን፡ አሰልጣኝ፡ይለማመዱ፡የነበሩት፡አበበ፡ቢቂላ፤ማሞ፡ወልዴ፤ዋሚ፡ብራቱ፤ደምሴ፡ወልዴ፤ሰብስቤ፡ማሞ፤ተገኝ፡በዛብህ፡አሁንም፡ልምምዳቸውን፡በመቀጠል፡በ1968ዓ.ም፡ወደ፡ሜክሲኮ፡ኦሎምፒክ፡በረሩ።
በሜክሲኮ፡ኦሎምፒከክ፡ለኢትዮጵያ፤ሌላ፡አዲስ፡ድል፡ተመዘገበ፡ማሞ፡ወልዴ፡በ10.000 ሜትር፡የብር፡ሜዳልያ፡አስገኘ፡በማራቶን፡ውድድር፡አበበ፡እና፡ማሞ፡አብረው፡ተሰለፉ፡በውድድሩ፡አጋማሽ፡ገደማ፡ጀግናው፡አበበ፡ህመም፡ስለተሰማው፡ወደ፡ማሞ፡ጠጋ፡ብሎ፡ማሞ፡ይህን፡ውድድር፡አሸንፈህ፡የሃገራችን፡ባንዲራ፡መውለብለቡን፡እምዲቀጥል፡አድርግ፡ብሎት፡ከውድድሩ፡ወጣ ፤ማሞም፡አደራውን፡ተቀብሎ፡አበበን፡በመተካት፡በቀዳሚነት፡ኦሎምፒክ፡ስታዲየም፡ደረሰ፡ሶስታኛው፡የማራቶን፡የወርቅ፡ሜዳልያ፡ለኢትዮጵያ፡ሆነ።
ማራቶን፡እና፡ኢትዮጵያ፡ኢትዮጵያ፡እና፡ማራቶን፡የማይነጣጠሉ፡የአንድ፡ሳንቲም፡ሁለት፡ገጽታዎች፡ሆኑ።ሶስት፡የኦሎምፒክ፡ማራቶን፡በተከታታይ፡ያአሸኘፈች፡ብቸኛ፡ሃገር፡እስከ፡አሁንም፡፡ኢትዮጵያ፡ብቻ፡ናት።

Sunday, March 23, 2008

የኢትዮጵያ፡አትሌቲክስና፡አትሌቶች፡ከየት፡ወዴት።

የአገራችን አትሌቶች የማይካፈሉበት ውድድር አይደምቅም እነሱ በደርሱበት ቦታ ሁሉ ባንዲራችን ክፍ ብላ ትውለበለባለች ይህቺ ሃገር በየዘመኑ ዓለምን የሚያስደንቅ ችሎታ ያላቸው አትሌቶች አጥታ አታውቅም፣፣
የሃገራችን አትሌቲክስ ስፖርት የተጀመረው በጦር ስራዊቱ አካባቢ እንደሆነ የሚጠቁሙ ብዙ ማረጋገጫዎች እናገኛልን
ከ1956 አውስትራሊያው ኦሊምፒክ ጫወታዎች ማግስት ጀምሮ ማራቶን የሚል ቃል በብዛት ይስማ ጀመር፣፣ ሁለተኛው የሃገራችን የ1960 የሮማ ኦሊምፒክ ግን ተሳትፎ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካም የመጀመሪያው ኦሊምፒክ ድል ሆነ ከዚያም መቀጠል በ1964 ቶኪዮ በራሱ ጀግናው በአበበ ቢቂላ ተደገመ የኢትዮጵያ ስም ሲነሳ ማራቶን የማራቶን ጉዳይ ሲነሳ ኢትዮጵያ የማይነጣጠሉ ሆኑ ከአራት ዓመት ቦሃላም ማሞ ሶስተኛውን የኦሊምፒክ ወርቅ ለሃገራችን አመጣ ማሞ በዚያ ብቻ አላበቃም በዘመኑ ነሃስም አስገኝቶልናል ፣፣
በእነ በሻይ ፈለቀ ገብረ የተጀመረው እነ አበበን ፣ ማሞን ፣ ደምስን ፣ሽበሺን፣ ተገኝ በዛብህን አስከትሎ ለነምሩጽ ይፍጠር ዘመን ስንደርስ ከማራቶን ወደ አስር አና አምስት  ሺህ ሜትር  በመሸጋገር   ኢትዮጵ ያዊያን  አትሌቶች  በየተሰለፉበት   የውድድ ር  መ ድረክ  ሁሉ  ድልን መቀዳጀት  የተለመደ  ሆነ ::