the green flood

the green flood

Saturday, May 11, 2013

የአትሌት ተወካዮች አትሌቱን መች ወክለው ያውቃሉ

         በተለያዩ ግዜያት  ችግራችሁን  ለመንግስት ለማሰማት ከፈለጋችሁ  የአትሌቶች  ተወካይ   ሊኖራችሁ  ይገባል
ተብለን  ከመካከላችን  ወከልን   ግን  እዚያ  ሲደርሱ የአትሌቶች  ተወካይ  መሆነቸው  ቀርቶ   በአትሌቱ   ላይ የመንግስት
ወኪል  ይሆኑና  ችግራችንን  ማድረሳቸው  ቀርቶ  እንዲያውም  እንድንፈራቸውና  ከመናገር  እንድንቆጠብ  ሆነናል
     ይህ  በተደጋጋሚ የታየ  ነገር ነው   ከኛ ጋር  ያላቸው  ግንኙነት  ከበላይ  መልእክት  ወይም አዲስ  ትእዛዝ ሲመጣ
ለመንገር ብቻ  ነው  ከተመረጡ  ቦኁላ አነጋገራቸውና  የሚጠቀሙአቸው  ቃላቶች  እንኳን  ሳይቀር   ከቀድሞው  የተለየ   እየሆነብን   ተቸገርን    ማን እነሱ   ፊት ይናገራል    ያስፈራል እኮ  እኛው መርጠን በእኛው ላይ  .....................

 ህዝቡ  ሁሉ አትሌቱ   የደላው  ምንም  ችግር  የሌለው  አድርጎ   ነው የሚያየው   ኧረ  ስንት ሰሚ  ያጡ  አሰልጣኞች እና
አትሌቶች   አሉ  አሁንማ  የቻለ  ይኮበልላል   ያልቻለው  ደግሞ   እውነተኛ  ተጠሪውን  እስኪመርጥ   እና  ሰሚ እስኪያ
ገኝ ድረስ  ዝምታን  መርጦአል  
  ቀን እስኪወጣልን   ድረስ  ሁኑ   ያሉንን  መሆን  ነው  ያለዚያማ  ይህቺ ገባ ወጣ  እያሉ  መቀራረምም  ትቀራለቻ   ሩጡ
ሲሉን  መሮጥ   ቁሙም  ከተባለ  መቆም    ስብሰባ  ላይም  ፊቱ   ፈታ ያላለ  ሰንበትበት  ብሎ  ነገር   ይመጣበታል  ያን
ፍራቻ  መሣቅ  ነው  ምን  እናድርግ    እንዲያውም    ሁሌ ለቅሶ  ቢኖር  እኮ እህህህህህ    ብለን   በሰበቡ   ይወጣል  ነበር