the green flood

the green flood

Saturday, August 12, 2017

ድንቅ አትሌቶቻችን አዲስ እና ፊጣ

አዲስ አበበ እና ፊጣ ባይሳ በበርካታ ዓለም አቀፍ እና የአህጉር ሻምፒዮናዎች ላይ ሃገራችንን በመወከል ተሰልፈው ድሎች የተቀዳጁ እጅግ ጠንካራ አትሌቶች ናቸው አዲስ አበበ እና ፊጣ ባይሳ በባርሴሎና ኦሊምፒክ ሁለቱም በየተሰለፉበት በ5000 እና በ10000 ሜትር ለኢትዮጵያ የነሃስ ሜዳሊያ ሲያስገኙ በሃቫናው iaaf world cup በሌጎስ እና በካይሮው የአፍሪካ ሻምፒዮናዎች እንዲሁም በካናዳው በዓለም ወጣቶች ሻምፒዮና ከዚያም በበርካታ የሃገር አቋራጭ እና የጎዳና ላይ ውድድሮች በተደጋጋሚ በማሸነፍ በወቅቱ ብዙ የተባለላቸው አትሌትች ናቸው ፊጣ በባርሴሎናው ኦሊምፒክ እንደሚያሸንፍ የዓለም የስፖርት ሚዲያዎች ከፍተኛ ግምት ከማግኘቱም በላይ በኮምፒዩተር ትንበያም ሳይቀር ድሉ የሱ እንደሚሆን ብዙዎች እርግጠኛ ሆነው ነበር ለውጤቱ አለመሳካት ከባርሴሎን መልስ በሰጠው ኢንተርቪው እንደተናገረው ( ምን እንደሆንኩ አላውቅም እግሬ ውሃ ሆነ ) ብሎ ነበር ለውጤቱ መበላሸ ምክንያቱ ግን በወቅቱ ኢትዮጵያ የነበረችበት ሁኔታ እና በአብዮታዊው መንግስት ሚዲያዎች ከልክ ያለፈ ከስፖርትነት አልፎ የኢትዮጵያን ስም ለማደስ እንደሚሮጥ መሸነፍ ጨርሶ የማይታሰብ እንደሆነ ይለፈፍ ስለነበረ ይህ ሁሉ ተደራርቦ የስነልቦና መረበሽ እንደፈጠረበ ግልጽ ነበር አዲስ አበበ በጣም ጠንካራ አትሌት ሲሆን በአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ውድድር በኢንዶኔዥያ ጃካርታ በተደጋጋሚ ያሸነፈ ከመሆኑም በላይ የርቀቱን ወሰን በመስበር በወቅቱ ከፍተኛውን የገንዘብ ሽልማት ያገኘ ባለትልቅ ዝና አትሌታችን ነው አዲስ በራሱ ጥረት እና በአሰልጠኝ ዶከተር ይልማ በርታ አባታዊ ምክር ስልጠና ድጋፍ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን አልፎ ለሃገሩ እና ለራሱ ክብርን የተቀዳጀ ጀግና ነው በዚህ አጋጣሚ ለመንግስት ለሚዲያዎች እና ለደጋፊዎች በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ከልክ ያለፈ ሃላፊነት በአትሌቶች ላይ መጫን በአትሌቶች ላይ መረበሽን እንደሚፈጥር እና አንዳንድ አትሌቶች ክልምምድ ቦኁላ በቂ እረፍት እንዳያደርጉ ይልቁንም በመኝታ እና በእረፍት ሰዓታቸው እንዲጨነቁ ብዙ እንዲያስቡ ስለሚያደርግ እና ይህ ደግሞ ጥሩ ላለመሮጣቸው ምክንያት ስለሚሆን አናስጨንቃቸው እላለሁ (የቻልከውን ያህል ሞክር ከዚያ በላይ አክርማ አይደለህ አትሰነጠቅ) ይል ነበር አሰልጣኝ ሻምበል ቶሎሳ ቆቱ አትሌቱ ነጻ ሆኖ በራሱ የበለጠ እንዲተጋሚያደርግ የስልጡን አባባል ነው

Saturday, July 1, 2017

ብርሃኑ ግርማ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ባለ ውለታ ነው

በጃን ሜዳ ላይ በብርሃኑ ግርማ አማካኝነት ተሰባስበው በአንድ ላይ ይለማመዱ ከነበሩት በመቶዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ ክለብ አትሌቶች መካከል ከግራ በኩል ግርማ ኡርጌ ፣ ታደሰ ከበደ ፣ወልደ አረጋይ ሁንዴ ፣ገረመው ፣ከሚል ፣ታደሰ አበበ ቢቂላ ፣መስፍን ዮሐንስ፣ መስፍን ጣሰው ፣አለማየሁ፣ተስፋዬ ዘለቀ፣ እና ፍቃዱ ይፍሩ ይገኙበታል
 በዚያን  ወቅት ብርሃኑ ግርማ በራሱ ፍላጎት ያለምንም  የደመወዝ ክፍያ ብዙ ወንዶች እና ሴት አትሌቶችን  ከመላው አዲስ አበባ ሰፈሮች ፣ ክለቦች  እና ትምህርት ቤቶች አንድ ላይ በማሰባሰብ በጃን ሜዳ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ  ሜዳዎች ላይ  በተለያዩ  ርቀቶች ከጀማሪ እስከ ከፍተኛ የብቃት ስልጠና ይሰጥ ነበር   የቀድሞው የኢትዮጵያ ባህር ኁይል  ኦፊሰር የሆነው ብርሃኑ ግርማ   
በአስር ሺህ እና በአምስት ሺህ  ሜትሮች እንዲሁም በሃገር አቋራጭ  ውድድሮች  በብዙ ኢተርናሽናል መድረኮች  የበርካታ ድሎች ባለቤት  የሆነ  ጀግና አትሌት ነው  ከነዚህም ውስጥ የሞስኮ ስፓርታኪያድ  እና ተከታታይ  ስድስት ዓመታት የአንጎላ ድሎቹ  ከብዙ አድናቂዎቹ አእምሮ  የማይጠፉ  ሲሆን  በዘመኑ  አረንጓዴው ጎርፍ( The green flood)የደጋው በራሪዎች ፣ የሰማይ ዳርቻ የማይበግራቸው  የሚል መጠሪያ የተሰጠው የጀግኖች አትሌቶች  ቡድን አካል ነበር 
ብርሃኑ ግርማ የኢትዮጵያን  አትሌቲክስ ስፖርት ለማሳደግ ክፍተኛ ድርሻ ካበረከቱት የስፓርቱ ባለውለታዎች ውስጥ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ያልተነገረለት  ጀግና ነው   በተለይም ለሴት አትሌቶች በብዛት ወደ ውድድር መድረክ መምጣት  ሰፊ መንገድ የከፈተ  ድንቅ አትሌት እና አሰልጣኝ  ነው  በአዲስ አበባ ክለቦች  ሻምፒዮና  እና በኢትዮጵያ ሻምፒዮናዎች  የሴት አትሌቶች  ቁጥር በአጭር ግዜ ጨምሮ ከወንዶች  እኩል  እንዲሆን  በግሉ ከፌዴሬሽኑ በላይ የሰራ ግን ምስጋና የተነፈገ  እንዲሁም  ስፖርቱን የበለጠ ተወዳጅ እና ተዘውታሪ  ለማድረግ በነበረው እቅድ በከተማችን የተለያዩ አካባቢዎች ውድድሮችን በማዘጋጀት የህዝቡን ተሳትፎ ለማጎልበት  በማሰብ ያቀረበው ጥያቄ  እኛም ከጎንህ አለን በርታ በማለት ፈንታ  ይህ የኛ ያልሆነ የባእዳን  ባህል  ነው  ውድድር  ከፌዴሬሽን ውጭ ማንም ማዘጋጀት አይችልም  በሚል ምላሽ እውቅናን  በመንፈግ ተስፋ አቆራጭ ምላሽ  የተሰጠው  የዛሬውን  የነ  ኍይሌን  ውድድር  ዓይነት  ገና ድሮ ያሰበ  እና  እድሉን ባይነፈግ  ኖሮ  ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ ሰው ይሆን ነበር 
  የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን  ለዘመናት ያዳበረው ክፉ ባህል ሆነና እንደነዚህ ያሉትን ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ  ታታሪ ሰዎችን  በማቅረብ ፈንታ ማራቅ  ስፖርቱን የሚጠቅሙትን  ሳይሆን በስፖርቱ የሚጠቀሙትን እና  የስርአቱ ደጋፊ የሆኑትን  ብቃት የሌላቸው ሰዎችን  በዙሪያው የሚሰበስብ  ቤት ስለሆነ  እንደነዚህ  ያሉ  ጠንካራ  ኢትዮጵያውያን  እድሉን ተነፍገው  የአትሌቲክስ  ስፖርታችን   እድገት  አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት እርምጃ ወደ ኋላ እያለ   እንዲኖር  ተደርጓል  

 



Saturday, March 28, 2015

Sunday, March 22, 2015

Friday, March 20, 2015

Saturday, March 7, 2015

Wednesday, August 14, 2013

በ1956 ዓ ም እኤአ የሜልቦርን ኦሊምፒክ በማራቶን ኢትዮጲያን ወክሎ የተወዳደረው በሻዬ ፈለቀ

ከሜክሲኮ  አደባባይ  ወደ ልደታ ሲኬድ ከተግባረ ዕድ  ወረድ ብሎ  ሞኤንኮ    በጥበቃ  ስራ ላይ  የነበሩት   አንጋፋ  አትሌት ለዚህ ሁሉ ድል እና ጀግንነት ፈር ቀዳጅ  እንደነበሩ  ሳስብ  እንደ ባለወርቅ  ሜዳሊያዎቹ  ጀግኖች ልቤ ያከብራቸዋል።
  ተግባረዕድ ስማር  ማታማታ እየሄድኩ አያቸው ነበር  ብዙ ታሪክ ይነግሩኝ ነበር ፡ የተረሱ  ጀግና  ናቸው ፡ ትዝ ከሚሉኝ ውስጥ ፡ አንድ ቀን  እንዲህ  አሉኝ  ፡ይሄውልህ  ልጄ ለመኖር መስራት  አለብህ  አለበለዚያ  ደግሞ ጥሩ  ውርስ  ሊኖርህ  ይገባል   ፡ይሄው  ለመኖር  ስል  ውርጭ  እየገረፈኝ  አድራለሁ ፡፡
 አትሌቲክስ  ፌዴሬሽንን  በተደጋጋሚ  ድጎማ እንዲያደጉልኝ  ጠይቄ  ተከለከልኩ  በመጨረሻ  ዘበኝነት  እንኳን  አስቀጥሩኝ   እና እዚሁ ካምቦሎጆ  ብርድ እና ጠሃዩ ይለብልበኝ  ቢያንስ  ቢያንስ  የምወደውን  ስፖርት  ሲለማመዱ አያለሁ ብዬ ለመንኩ ፡  ኧረ ተወው ልጄ ብለው ድንገት ትክዝ ብለው ቀሩ ፡ ባሻዬ  ምነው  ስላቸው ፡ ባዘነ ፊት ቀና ብለው   እነ እከሌ  አልልህም   ይሸሹኝ  ጀመር  ብቻ አንድ ሰው አለ  ነፍሱን ይማረውና  ያ  ይድነቃቸው  ተሰማ  የትም  ይየኝ  አክብሮ  ሰላም ብሎኝ ፡  ትቶኝ ይሄድ መሰለህ ፡ እቤቱ  ወስዶኝ   በእጄ ብሎኝ  ከቁምሳጥኑ መዞ ሙሉ ልብስ  ከጫማ ጋር  ሸልሞኝ  ይሸኘኛል   ብለው  አሁንም  ትክዝ  አሉ ፡፡
  በአጋጣሚ  አስተማሪ የሌለ  ቀን  ወይም በእረፍት ሰዓት ሁሌ ወደ እሳቸው  ጋር እሮጣለሁ  እኔም እሮጥ ስለነበረ  በስፖርቱ ዙሪያ  የሚነግሩኝ  ነገር እና ምክራቸው ይስበኛል ፡በዚያ ወቅት  እኔ በትንሽ  የኪስ ገንዘብ  የምሮጥ  እና ከዚያችው  ከፍዬ  የምማር  ስለነበር ልረዳቸው  ባለመቻሌ  አዝን ነበር ፡፡
  ስፖርተኛ እና አዳኝ  አንድ ነው በለስ የቀናው  እለት ይዞ ይገበል  ጉሮወሸባ  ይባልለታ    ያልቀናው ቀን ደግሞ  ዝም  ነው  ፡ ስለዚህ  ስትሸነፍ ብዙ አትዘን  ሌላ ቀን አለና ፡፡እንዲ አይነቱ ለዛ ያለው ምክራቸው ነበር  የሚስበኝ፡ ይህ ከሆነ 22 ዓመታት አልፎልታል


               ነባር አትሌቶች እና እንደ ስንታየሁ እና ገብሬ   ያሉ እንዲሁም አትሌቶች  በድል ሲመለሱ  ከዱሮ ጀምሮ  በከፍተኛ  ወጭ አቀባበል  ሲያደርጉና  በብዙ ነገር  ጀግኖችን  ሲያስታውሱ  የኖሩትን እንደ አቶ አብይሴሎም  ያሉ  የሃገራችን አትሌቲክስ ባለውለታ የሆኑትን   በአንዳንድ  ዓለም አቀፍ የውድድ መድረኮች ላይ  ለንግድ ከሚጓዙ ኮሚቴዎች  ቁጥር ቀነስ በማድረግ በክብር ተጋባዥነት  አልፎ አልፎ ቢሄዱ ውለታቸው በመጠኑ ተከፈለ ማለት ነው  እና   ይታሰብበት አደራ ፡፡